ቴክኖቢዚያ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ኢንተርፕራይዝ ለሠራተኞች የትንሳኤ በአል መዋያ ስጦታ አበረከተ።
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የቴክኖቢዚያ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ኢንተርፕራይዝ "እያመረተ ለማሰልጠን" የተቋቋመ ኢንተርፕራይዝ ነው። ኢንተርፕራይዙ የትንሳኤ በአልን ምክንያት በማድረግ 1.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የበአል መዋያ ስጦታ ለ194 ሰራተኞች አበርክቷል። ይህም ኢንተርፕራይዙ ከቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ስራዎች በተጨማሪ በማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ እየተሠማራ እንደሆነ ማሳያ ነው ሲሉ የኢንተርፕራይዙ ሥራ አስኪያጅ አቶ ለሚ ቱጆ ገልጸዋል። ቴክኖቢዚያ የኢንደስትሪ ውጤቶች ኢንተርፕራይዝ የኢንስቲትዩቱ ተልዕኮዎች የሆኑትን ስልጠናን፣ ጥናትና ምርምርን እና የቴክኖሎጂ ፈጠራን ለማስተሳሰር እየሰራ ይገኛል። በአሁኑ ሰአት በአገራችን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እንዲመረቱ፣ በስፋትም ወደ ተጠቃሚዎች እንዲደርሱ በስፋት እየሰራ ያለ ተቋም ሆኗል።