Technical and vocational training is a sector that fulfills the mission of producing competent
human resources in a universal manner and providing technologies that improve production and productivity. From the point of view of the sector, the current period requires
us to be competitive in the international market in addition to meeting domestic
demand by increasing production and productivity by providing important industrial inputs and
products which are diverse and market oriented.
In addition to the mission of producing trainers and leaders who make technical and vocational
training institutions effective as well as skilled industrial technicians,
the Institute of Technical and Vocational Training of the Federal Republic of Ethiopia, has
created a new concept of “Technical and Vocational Training beyond Training” in
order to satisfy its new mission.
more
info
የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የቴክኖቢዚያ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ኢንተርፕራይዝ "እያመረተ ለማሰልጠን" የተቋቋመ ኢንተርፕራይዝ ነው። ኢንተርፕራይዙ የትንሳኤ በአልን ምክንያት በማድረግ 1.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የበአል መዋያ ስጦታ ለ194 ሰራተኞች አበርክቷል። ይህም ኢንተርፕራይዙ ከቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ስራዎች በተጨማሪ በማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ እየተሠማራ እንደሆነ ማሳያ ነው ሲሉ የኢንተርፕራይዙ ሥራ አስኪያጅ አቶ ለሚ ቱጆ ገልጸዋል። ቴክኖቢዚያ የኢንደስትሪ ውጤቶች ኢንተርፕራይዝ የኢንስቲትዩቱ ተልዕኮዎች የሆኑትን ስልጠናን፣ ጥናትና ምርምርን እና የቴክኖሎጂ ፈጠራን ለማስተሳሰር እየሰራ ይገኛል። በአሁኑ ሰአት በአገራችን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እንዲመረቱ፣ በስፋትም ወደ ተጠቃሚዎች እንዲደርሱ በስፋት እየሰራ ያለ ተቋም ሆኗል።
በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ቴክኖቢዚያ የኢንደስትሪ ውጤቶች ኢንተርፕራይዝ የበጀት ዓመቱን የ6 ወራት ዕቅድ ፈጻጸም ለቦርዱ አቅርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡ ኢንተርፕራይዙ የያዛቸው ፕሮጀክቶች አፈጻጸም፣ የመደበኛ ስራዎች ዕቅድ አፈጻጸም የውይይት አጀንዳ ሲሆኑ የኦዲት ሪፖርትም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ እና የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳሬክተር ዶ/ር ብሩክ ከድር ከተመሰረተ አንድ ዓመት የሞላው ኢንተርፕራይዙ ከምስረታ እና የዝግጅት ጊዜ አልፎ በርካታ ተግባራትን መፈጸም መቻሉን ገልጸዋል፡፡ ኢንተርፕራዙ ለመሰል ተቋማት ሞዴል ተቋም እንዲሆን ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል። የኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂ እና ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጸዳለ ተክሉ በበኩላቸው ኢንተርፕራይዙ ሲቋቋም የተለመዱ ስራዎችን ለመስራት ሳይሆን በዘርፉ አዲስ ባህል ለመፍጠር ነው ብለዋል። በዚህ አንድ ዓመት ውስጥ ከውጪ የሚገቡ ቴክኖሎጂዎችን ማምረት መቻሉ ትልቅ እመርታ ነው ያሉት ም/ዋና ዳይሬክተሯ በተለያዩ መለኪያ መስፈርቶች ተወዳዳሪነቱን ማጠናከር አለበት ብለዋል። የኢንተርፕራይዙ ስራአስኪያጅ አቶ ለሚ ቱጆ ባለፉት ስድስት ወራት የተፈጸሙ ተግባራት ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም በማኑፋክቸሪንግ፣ በኮንስትራክሽን፣ በአገልግሎት ዘርፎች የተከናወኑ ስራዎችን አቅርበል፡፡ እንደአገር የመጀመሪያ የሆነ የተሸከርካሪ ጎማ መልሶ ጥቅም ላይ የሚያውል ፋብሪካ በራስ አቅም ተሰርቶ ወደስራ መግባቱን በትልቁ የጠቀሱት አፈጻጸም ነው፡፡ ቴክሎጂዎችን በስፋት የማምረት ስራ የተጀመረ ሲሆን በቀጣይም ሌሎች ላይ ለመስራት የቴክኖሎጂ ልየታ መካሄዱን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ረጃጅም ወንዞችን የሚሻገሩ ተንጠልጣይ ድልድዮችን ሰርተው ለተጠቃሚው ማድረስ መቻሉንም ስራአስኪጁ በሪፖርታቸው ገልጸዋል። በሥራናክህሎት ሚኒስቴር በኩል ለዓለምአቀፍ የስራ ገበያ ብቁ የሆኑ ሾፌሮችን የማሰልጠን ስራ እየተሰራ መሆኑም ሌላው ኢንተርፕራይዙ በስኬት ከፈጸማቸው ተግባራት መካከል ተጠቅሷል፡፡ "እያመረትን እናሰለጥናለን" በሚል መርህ የተቋቋመው ኢንተርፕራይዙ ይህንኑ ተልዕኮ ለማሳካት ከኢንስቲትዩቱ ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ መሆኑ ገልጸው ይበልጥ ትስስሩን ለማጠናከር የአሰራር ማንዋል የተዘጋጀ ሲሆን በቀጣይ ለቦርድ ይቀርባል ብለዋል። በጋርመንት እና ሌዘር ዘርፎ የተማሪዎች ዩኒፎርም ማምረት፣ ቦርሳ ማምረት እንዲሁ ከበርካታ የፕሮጀክት አፈጻጸሞቹ መካከል የተነሳ ነው፡፡ የቦርድ አባላትም ኢንተርፕራይዙ በአጭር ጊዜ ትልቅ ትምህርት ሊወሰድበት የሚችል አፈጻጸም መፈጸም መቻሉን አድንቀው ይበልጥ ሊጠናከር ይገባል ያሏቸውን ሐሳቦች አንስተዋል። በመጨረሻም የቦርዱ ሰብሳቢ ዶ/ር ብሩክ ከድር እስከ ቀጣዩ የቦርድ የግንኙነት ጊዜ ሊሰሩ ይገባል ያሏቸውን አቅጣጫዎች አስቀምጠው ውይይቱ ተጠናቅቋል።
Our enterprise has signed an agreement for the establishment of Training and Entrepreneurship Development Excellence Center as part to Consultancy Services which also includes facility design at Productivity Improvement Center with AA Bureau of Labor and Skills.